በእንጅባራ ከተማ በ124 ሚሊየን ብር የተገነቡት መሠረተ ልማቶች ለአገልግሎት ክፍት ኾኑ።

47

ባሕር ዳር: ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በእንጅባራ ከተማ አስተዳደር በ2015 ዓ/ም በ124 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነቡ መሠረተ ልማቶች የክልል፣ የብሔረሰብ አሥተዳደር፣ የወረዳና የከተማ አሥተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና የእንጅባራ ከተማ ነዋሪዎች በተገኙበት ተመረቀው ለአገልግሎት ክፍት ኾነዋል ።

የተመረቁ መሠረተ ልማቶች ፦

በቀበሌ አንድ መንታ መንገድ ኮብል፣ በቀበሌ አራት ኮብል መንገድ ፣ በቀበሌ አምስት ሁለት የወጣቶች መዝናኛ ማዕከላትና ሌሎችም ግንባታቸው የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መመረቃቸውን የአዊ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል ።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአልማ በእብናት ወረዳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ያስገነባው ባለ ሦስት ፎቅ የመማሪያ ህንፃ ተመረቀ።
Next article“ያጋጠሙና ሊያጋጥሙ የሚችሉ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ችግሮችን ለመፍታት መረጃንና ማስረጃን መሠረት ያደረገ ተግባር እና ውሳኔ ማድረግ ያስፈልጋል“ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር