አልማ በእብናት ወረዳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ያስገነባው ባለ ሦስት ፎቅ የመማሪያ ህንፃ ተመረቀ።

26

ባሕር ዳር: ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ጎንደር ዞን አልማ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት በእብናት ወረዳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ባለ ሦስት ፎቅ የመማሪያ ህንፃ በመንግስት እና በሕዝብ ተሳትፎ ተገንብቷል።
ለግንባታው 21 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ወጭ ተደርጓል።

ህንጻውን የአልማን ሳምንት ምክኒያት በማድረግ ከፍተኛ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ አመራሮች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ በተገኙበት መመረቁን የደቡብ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚታዩ ሐሰተኛ መረጃዎች ለመደበኛው የመገናኛ ብዙኃን እና ለጋዜጠኞች ፈታኝ እየኾኑ መምጣቸው ተገለጸ።
Next articleበእንጅባራ ከተማ በ124 ሚሊየን ብር የተገነቡት መሠረተ ልማቶች ለአገልግሎት ክፍት ኾኑ።