
ባሕር ዳር: ሐምሌ 16/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኀላፊ ኃይለማርያም ከፍያለው (ዶ.ር) ወቅታዊ የክረምት የግብርና ሥራዎችን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ዘዴዎችን ቆጥረን ይዘን በቁርጠኝነት ተግባራዊ ካደረግናቸው በምርት ዘመኑ ያቀድነውን 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት አሟጦ በዘር መሸፈን፣ አማካይ ምርታማነትን በሄክታር 31 ነጥብ 8 ኩንታል ማድረስ እና 160 ሚሊዮን ኩንታል ማምረት በእርግጥም እናሳካዋለን ብለዋል።
ከማን፣ ምን እንደሚጠበቅ ዝርዝር ተግባራትን ያነሱት ዶክተር ኃይለማርያም የሚከተሉት አንኳር ጉዳዮች ገቢራዊ እንዲኾኑ አሳስበዋል።
🌾የሰው ሀይሉን በሙሉ አቅም ስምሪት መስጠት፣
🌾ተልዕኮን የመፈፀም ብቃት ማሳደግ
🌾በየስራ ዘርፉ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት መረባረብ
🌾ችግርን በራስ አቅም የመፍታት ልምምድን ማዳበር
🌾አቅዶ የሚፈፅም ጠንካራ ተቋም መፍጠር
🌾በጊዜ ሰሌዳና አግሮ ኢኮሎጂን መሰረት አድርጎ መንቀሳቀስ
🌾ተከታታይነት ያለው የድጋፍና ክትትል ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገበባ ገልጸዋል።
መረጃው የአማራ ግብርና ቢሮ ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!