የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ ጡት የሚያጠቡ ሴት ተፈታኞች ሞግዚት ይዘው እንዲገቡ ተፈቀደ።

65

ባሕር ዳር: ሐምሌ 16/2015 ዓ.ም (አሚኮ) መውለጃ ወራቸው የደረሰ ነፍሰ ጡርና ጡት የሚያጠቡ ሴት ተፈታኞች በሚቀጥለው ዓመት ተዘጋጅተው እንደ መደበኛ ተፈታኝ መፈተን እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ፡፡

ይሁን እንጂ ፈተናውን ለመፈተን ዝግጁ ከሆነ ጡት የሚያጠቡት ተፈታኞች አንድ ሴት ሞግዚት ይዘው በመግባት እንዲፈተኑ ተገቢው ድጋፍ የሚደረግላቸው መሆኑን ገልጿል።

የተፈታኞች መብትና ግዴታ እንዲሁም የተከለከሉ ነገሮች በተፈታኟና በሞግዚቷ ላይ ተግባራዊ እንደሚሆኑ ገልጿል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleግርማዊ ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለሥላሴን የሚዘክር ሀውልት በአዲስ አበባ አማካይ ቦታ ላይ እንዲገነባ ተጠየቀ።
Next article“ዕውቀታችሁን ወደተግባር በመለወጥ ታሪካዊ ኀላፊነታችሁን ልትወጡ ይገባል” የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ከፍያለው አለማየሁ