“ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ ናት” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ

39

ባሕር ዳር: ሐምሌ 14/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ዳይሬክተር ዋንግ ዪ ጋር ተወያይተዋል።

ዋንግ ዪ ከቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ የተላከ መልዕክትም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ ገልጸዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ዳይሬክተር ዋንግ ዪ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ አዲስ አበባ ገቡ።
Next articleየአማራ ክልል የ2016 በጀት ዓመት ጠቅላላ በጀት 137 ቢሊዮን 408 ሚሊዮን 472 ሺህ 187 ኾኖ ጸደቀ።