
እንጅባራ: ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በምርቃ መርሃ ግብር ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ጋርዳቸው ወርቁ ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታ ያገኙትን ጥበብ፣ የአላማ ፅናትና ጥንካሬ በመጠቀም ሕዝቡን በቅንነትና በታማኝት እንዲያገለግሉ መልእክት አስተላልፋዋል።
ዩኒቨርሲቲው 750 ተመራቂዎችን ማስመረቁንም ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከ2010 ጀምሮ በመማር ማስተማር ፣ በጥናትና ምርምር ሰፊ ሥራዎችን እየሠራ ነው ፤ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በምረቃ ፕሮግራሙ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው “ጂጂ” የክብር ዶክትሬት ሠጥቷል፡፡
ዘጋቢ፡- አዳሙ ሽባባው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!