ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና ተከታታይ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎች ለ4ኛ ዙር እያስመረቀ ነው።

48

ደባርቅ: ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም (አሚኮ)ዩኒቨርሲቲው በ 4 ኮሌጆች በ 21 የትምህርት ክፍሎች በመደበኛ የትምህርት መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎች ለ4ኛ ዙር ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

በዕለቱ በተከታታይ የትምህርት መርሐ ግብር ያስተማራቸው የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪዎቹንም እያስመረቀ መኾኑን ከዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ የኢትዮጵያ ፕሮፌሰሮች ካውንስል አባል እና ሲኒየር ተመራማሪ እና የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ዓለማየሁ ቢሻው (ፕሮፌሰር)፤ የራያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ታደሰ ደጀኔ (ዶ.ር)፤ የአማራ ክልል የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ሴክሬታሪያት አስማረ ደጀን (ዶ.ር)፤ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት መስራች አበጀ ታፈረ (ዶ.ር)፤ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞው የአሥዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት መስራች አወቀ በላይ (ዶ.ር) እና ሌሎች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።

ዘጋቢ:-አድኖ ማርቆስ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በማታ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ከ2 ሺህ 100 በላይ ተማሪዎች እያስመረቀ ይገኛል።
Next article“በደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በአጼ ተዎድሮስ ስም በተሠራው ሮኬት የተደረገው የተሳካ ሙከራ ኢትዮጵያን በህዋ ምህንድስና ስሟ እንዲጠራ ያደረገ ነበር” አነጋግረኝ ጋሻው (ዶ.ር)