የአማራ ክልል ምክር ቤት የ6ኛ መደበኛ ጉባኤውን የሁለተኛ ቀን ውሎ ጀምሯል።

109

ባሕር ዳር: ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ምክር ቤት ከሐምሌ 12 እስከ 14/2015 ዓ.ም የሚካሄደውን 6ኛ ዙር፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 6ኛ መደበኛ ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎውን ጀምሯል። በመጀመሪያ ቀን የምክር ቤቱ ውሎ ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) የክልሉን አስፈጻሚ አካላት እቅድ አፈጻጸም የተጠቃለለ ሪፖርት አቅርበው ጥያቄና አስተያየቶች ከአባላቱ እየቀረቡ ነበር።

ከምክር ቤት አባላት የሚቀርቡ ጥያቄ እና አስተያየቶች በዛሬ ጥዋት የምክር ቤቱ መርሐ ግብርም ቀጥለዋል።

ከአስተያየት እና ጥያቄዎች በኋላ አስፈጻሚ አካላት ተጨማሪ ማብራሪያ እና ምላሾችን እንደሚሰጡም ይጠበቃል። በምክር ቤቱ ውሎ የሚነሱ ዋና ዋና ጉዳዮችን አሚኮ ኦንላይን ለተከታታዮቹ ያደርሳል።

ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው የአርት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥ በዛሬው ዕለት ይከናወናል።
Next articleየደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በማታ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ከ2 ሺህ 100 በላይ ተማሪዎች እያስመረቀ ይገኛል።