“አሁን የተገኘውን ሰላም በማጽናት የበለጠ የልማት ሥራ እንደሚሠራ አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ።

16

ባሕር ዳር: ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በትግራይ ክልል በአንድ ቀን 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በተገኙበት ነው እየተካሄደ ያለው።

አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ባደረጉት ንግግር አሁን የተገኘውን ሰላም በማጽናት የበለጠ የልማት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

ሰላሙን ለማጽናት የፌዴራል መንግሥት ጠንክሮ እየሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የክልሉ ጊኤአዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፤ ሰላም ሰፍኖ ወደዚህ አይነት ተግባር መመለስ መቻሉ መልካም መሆኑን በመጥቀስ፤ የተገኘውን ሰላም ለማጽናት ጠንክረው እንደሚሰሩ አብራርተዋል።

በመላው አገሪቱ ከጠዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ እስከ 5:30 ባለው ሰዓት 247 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት መግለጹ ይታወሳል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ግብን ለማሳካት ሁሉም ዜጋ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል” የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባዔ አገኘሁ ተሻገር
Next articleከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ እየገጠመን ያለውን ችግር ለመቀነስ በአረንጓዴ አሻራ ላይ የጀመርነውን ስራ እናጠናክራለን -አቶ ሽመልስ አብዲሳ