በሞጣ ካጋጠመው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ 15 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ፤ ከተማዋ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ መለሷም እየተነገረ ነው፡፡

181

በሞጣ ካጋጠመው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ 15 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ፤ ከተማዋ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ መለሷም እየተነገረ ነው፡፡

ከዛሬ ማለዳው ጀምሮ መደበኛ የከተማዋ እንቅስቃሴ ቀጥሏል፡፡ አንዳንድ የንግድ ተቋማት ሥራ ጀምረዋል፡፡ ከተማዋ ከባሕር ዳር – አዲስ አበባ የሚያልፈው ዋና መስመር ላይ እንደመሆኗ ሀገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎች ከሌሊት ጀምሮ ነበር መደበኛ እንቅስቃሴ የተጀመሩት፡፡ ዞር ዞር ብለን በተመለከትናቸው ቤተ እምነቶች አካባቢ ግን የነበረው ችግር ድባብ ሙሉ በሙሉ የተቀረፈ አይመስልም፡፡

ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አያልነህ ተስፋዬ ባገኘነው መረጃ መሠረት እስካሁን 15 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ አካባቢውን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለስ የማድረጉ እና ተጠርጣሪዎችን እየለዩ በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሥራም ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

ዘጋቢ፡- የማነብርሃን ጌታቸው -ከሞጣ

Previous article“ማንኛውም ፈተና የአማራን ሕዝብ ሊያንንበረክከው አይችልም።” የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት
Next articleባሕር ዳር ከነማ በመጀመሪያው አጋማሽ የነበረበትን ክፍተት በሁለተኛው አጋማሽ ማረሙ ውጤት እንዳስገኘው አሰልጣኙ ተናገሩ፡፡