
ባሕር ዳር: ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል በአንድ ጀንበር 260 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል መርሃ ግብር በሁሉም ዞኖች በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ከንጋት ጀምሮ እየተከናወነ የሚገኘው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በ 128 ወረዳዎች፣ በ 1690 ቀበሌዎች እየተከናወነ ነው።
እስከ ጠዋቱ 4 ሰዓትም 12 ሺ 148 ሄክታር መሬት በችግኝ የተሸፈነ ሲሆን 105 ሚሊየን 152 ሺ 813 ችግኞች ተተክለዋል።
በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሳታፊ ወንድ 1 ሚሊየን 408 ሺ 462 ሴት እና 565 ሺ 549 በድምሩ 1 ሚሊየን 974 ሺ 11 ሰዎች ተሳትፈውበታል።
መረጃው የአማራ ኮሙኒኬሽን ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
