
ባሕር ዳር: ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል በአንድ ጀምበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡
ዘመቻው ከጥዋቱ 12 ሠዓት ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተጀመረ ሲሆን ቀኑን ሙሉ የሚቀጥል ነው ተብሏል።
እስከ ምሽት 12 ሰዓት ድረስ በሚቆየው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር 260 ሚሊየን የችግኝ መትከያ ጉድጓድ እንደተዘጋጀም ተጠቅሷል፡፡
26 ሺህ ሄክታር መሬት በችግኝ እንደሚሸፈን እና በዕለቱም 5 ሚሊየን ሕዝብ በችግኝ ተከላው እንደሚሳተፍ ተጠቁሟል፡፡
በክልሉ በአንድ ጀምበር 260 ሚሊየን ችግኝ እንደሚተከል ተመላክቷል።
የከተማው ነዋሪዎች በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ ላይ እየተሳተፉ ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
