“ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደኅንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት ሀገር እንገነባለን” ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ

46

ባሕር ዳር: ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም (አሚኮ) “ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን” ሲሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ ገለጹ።
በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው መርሐ-ግብር መሰረት ኢትዮጵያዊያን በነቂስ ወጥተው ችግኝ እየተከሉ ነው።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያዊያን ዝናቡ ሳይበግራቸው ችግኝ በመትከል ላይ ይገኛሉ።

ችግኝ መትከል የሕልውና ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በድርቅ የምትጠቃ ሀገር በመሆኗ አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ከመትከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዳይ ነው ብለዋል።

“ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን” ብለዋል ሚኒስትሩ።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃግብርን በአዲስ አበባ አስጀመሩ።
Next articleበአማራ ክልል በአንድ ጀምበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዘመቻ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ዘንዘልማ ቀበሌ ገላድ ተፋሰስ አካባቢ ተጀምሯል።