የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ማታ ጀምሮ መመልከት ይችላሉ – የትምህርት ሚኒስቴር

119

ባሕር ዳር: ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በማጠናቀቅ ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ማታ ጀምሮ መመልከት እንደሚችሉ አስታውቋል።

በዚህም ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ እሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ በ https://result .ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ እንደሚችሉ ተገልጿል።

በመውጫ ፈተናው የሚፈለገውን የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ፈተናውን በየስድስት ወሩ ደጋግመው መውሰድ እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።

የመውጫ ፈተናው ከመሰጠቱ አስቀድሞ ተመራቂ ተማሪዎች ከፈተና ሥርዓቱ ጋር እንዲለማመዱ የሙከራ እና የሞዴል ፈተና እንዲወስዱ መደረጉ ይታወሳል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከተጀመሩ ሪፎርሞች አንዱ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበብቸና ከተማ አሥተዳደር ከ98 ሚሊዮን ብር በላይ በኾነ ወጪ የተገነቡ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ኾኑ።
Next articleባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች ውስጥ 84.7 በመቶ 50% እና ከዚያ በላይ በማምጣት ማለፋቸውን አስታወቀ።