የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዝግጅት ማጠናቀቁን የምዕራብ ጎጃም ዞን ገለጸ።

30

ፍኖተ ሰላም: ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (አሚኮ) “ነገን ዛሬ እንትከል”በሚል መሪ መልዕክት ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዝግጅቱ መጠናቀቁን የዞኑ ግብርና መምሪያ ኀላፊ ጥላሁን አለምነህ ለአሚኮ ገልጸዋል።

የዞኑ ግብርና መምሪያ ኀላፊ ጥላሁን አለምነህ እንደገለጹት፦

🌱 በአንድ ጀንበር የሚተከል 29 ነጥብ 9 ሚሊዮን ችግኝ ተዘጋጅቷል

🌱 2 ሺህ 991ሄክታር መሬት ለተከላ ተለይቷል

🌱 30 ሚሊዮን የሚጠጋ የችግኝ ጉድጓድ ተዘጋጅቷል

🌱 ለችግኝ ተከላዉ ከ800 ሺህ በላይ የማኅበረሰብ ክፍል ይሳተፋል ተብሎ ይጠበቃል

🌱 በዞኑ በወረዳዎችና ከተማ አሥተዳደሮች በ397 ቀበሌ በ816 የተከላ ቦታ የአንድ ቀን ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ ይከናወናል።

🌱 በዞኑ በተያዘው የክረምት ወቅት በጠቅላላው 206 ሚሊዮን የሚጠጋ የደንና ፍራፍሬ ችግኝ ለመትከል መታቀዱን የዞኑ ግብርና መምሪያ ለአሚኮ አስታውቋል።

ዘጋቢ:- ዘመኑ ይርጋ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleለአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ 28 ነጥብ 4 ሚሊዮን ችግኞችን ማዘጋጀቱን የደቡብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ፡፡
Next article“አስፈጻሚ ተቋማት አካቶ ትግበራን በልኩ ተፈጻሚ እንዲያደርጉ ኀላፊነታችንን እንወጣለን” ወይዘሮ አበራሽ ታደሰ