ለሐምሌ 10/2015 ዓ.ም የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ ዝግጅት መጠናቀቁን የምሥራቅ ጎጃም ዞን ገለጸ።

67

ደብረማርቆስ : ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኅላፊ አበበ መኮንን “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ መልዕክት ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም ለሚካሄደው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዝግጅት መጠናቀቁን ለአሚኮ ተናግረዋል።

እንደ ዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኅላፊ ገለጻ፦

🌳 በአንድ ጀንበር የሚተከሉ 33 ነጥብ 18 ሚሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል፡፡

🌳 319 ሄክታር መሬት ለተከላ ተለይቷል።

🌳 33 ሚሊዮን የችግኝ ጉድጓድ ተዘጋጅቷል።

🌳 ለችግኝ ተከላዉ ከ660 ሺህ በላይ የማኅበረሰብ ክፍል ይሳተፋል።

🌳 በዞኑ በከተማ እና በገጠር የሚኖረዉ ማኅበረብ እና ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ።

🌳 በዞኑ በተያዘው የክረምት ወቅት 252 ሚሊዮን 119 ሺህ ችግኝ ለመትከል ታቅዷል።

🌳 እስካሁን ባለው ጊዜም በዞኑ በ17 ወረዳዎች በ318 ቀበሌዎች በ2 ሺህ 356 የተከላ ቦታ 6 ሺህ 771 ነጥብ 8 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቷል።

🌳 በዞኑ በ2014 ዓ.ም ከተተከለው 277 ሚሊዮን ችግኝ 80 በመቶ የሚሆነው መጽደቅ ችሏል።

ዘጋቢ፦ ንጉስ ድረስ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብርን ስኬታማ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
Next article“መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጠዋት 12፡00 ጀምሮ እስከ ምሽት 12፡00 ድረስ አሻራውን በኢትዮጵያ ካርታ ላይ ያሳርፍ” ግርማ አመንቴ (ዶ.ር)