የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የመደበኛ ፖሊስ አባላትን እያስመረቀ ነው።

94

ባሕር ዳር: ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ በጥሩ ብርሃን መሠረታዊ ፖሊስ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዛሬ እያስመረቃቸው የሚገኙት በልዩ ኃይል ፖሊስነት ሲያገለግሉ ቆይተው ስልጠና በመውሰድ የመደበኛ ፖሊስ አባል የሆኑ የቀድሞ የአማራ ልዩ ኃይል አባላትን ነው።

ስልጠናውን አጠናቅቀው የምረቃ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

በምረቃ ሥነሥርዓቱ የተገኙት የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደጀኔ ልመንህ ለተመራቂዎች ሀገርን ከጠላት በመከላከል ታላቅ ጀግንነት እንደፈፀማችሁ ሁሉ የክልሉን ሕዝብ ሰላም እና አንድነት ማስጠበቅ ይገባቹሃል ብለዋል።

ዘጋቢ፦ተመስገን ዳረጎት

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ።
Next article“ዓላማችን ሪከርዳችንን መስበር ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)