የሴቶች ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ኤርጎጌ ተስፋየ (ዶ.ር) በደቡብ ጎንደር ዞን ተገኝተው ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አሳረፉ።

111

ባሕር ዳር: ሐምሌ 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ወጅ ቀበሌ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ተካሄዷል። በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላው የሴቶች ሕጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋየ ተገኝተው አሻራቸውን አሳርፈዋል።

በችግኝ ተከላው ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሚኒስቴር ዴኤታ መክዩ መሐመድ፣ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኀላፊ ኃይለማርያም ከፍያለው (ዶ.ር) እና ሌሎችም የፌደራል፣ የክልል እና የዞን የሥራ ኀላፊዎች አሻራቸውን አሳርፈዋል።

ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአቶ አህመድ ሽዴ የተመራው የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ ባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት ላይ ነው።
Next articleየክልል ክለቦች ሻምፒዮናው ግማሽ ፍጻሜ ላይ ደርሷል!!