በምርት ዘመኑ 2 ሚሊዮን ኩንታል ሩዝ ለማምረት እየተሠራ መኾኑን የደቡብ ጎንደር ዞን ገለጸ፡፡

52

ባሕር ዳር: ሐምሌ 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የ2015/2016 ምርት ዘመን የሩዝ ክላስተር ዘር ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦከምከም ወረዳ እየተካሄደ ነው። በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች የሩዝ ኩታ-ገጠም ዘሩን አስጀምረዋል።

ኩታ-ገጠሙ የሚገኘው በወረዳው ቡራ ቀበሌ ሲኾን በዚሁ ቀበሌ ብቻ 482 ሄክታር መሬት ሰብል ይሸፈናል ተብሏል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ኀላፊ አዲስ ተፈራ በዚህ ዓመት 50 ሺህ ሄክታር ሩዝ በኩታ-ገጠም ለማልማት እየተሠራ ነው ብለዋል። እስካሁን ድረስም 80 በመቶው መሬት በዘር ስለመሸፈኑ አስረድተዋል። በ2015/2016 የምርት ዘመን 2 ሚሊዮን ኩንታል ሩዝ ለማምረት መታቀዱንም ገልጸዋል።

ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በአማራ ክልል ከደረጃ በታች ያሉ ትምህርት ቤቶችን ታሪክ ለማድረግ እየሠራን ነው” ማተብ ታፈረ (ዶ.ር)
Next article“በአማራ ክልል 17 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዜጎችን የጤና መድኅን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል” ዶክተር መልካሙ አብቴ