
ባሕር ዳር: ሐምሌ 01/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ተቋማትና ድርጅቶች ለገበታ ለትውልድ የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደቀጠሉ ነው።
በ16ኛው ዙር የተለያዩ ተቋማት ከ76 ሚሊዮን ብር በላይ ለገበታ ለትውልድ ድጋፍ ማድረጋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።
በዚህም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን 30 ሚሊዮን ብር፣ የፔትሮሊየም አቅራቢ 26 ሚሊዮን 822 ሺህ 668 ብር፣ መኪያ ኢንተርፕራይዝ 10 ሚሊዮን ብር፣ የኬሚካል ኢንዱስትሪያል ኮርፖሬሽን 6 ሚሊዮን 432 ሺህ 335 ብር እንዲሁም ጌቱ ገለጠ 5 ሚሊዮን ብር ለገበታ ለትውልድ ለግሰዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!