ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ

38

ባሕር ዳር: ሰኔ 30/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ሞኒክ ሳንዛባጋንዋ (ዶ.ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ምክትል ሊቀመንበሯ አሁን ላይ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እየተካሄደ ስላለው ማሻሻያ በተመለከተ ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገላጸ አድርገዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠውላቸዋል፡፡

ኮሚሽኑ ለሚያካሂደው የማሻሻያ ሥራ ኢትዮጵያ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኗን መግለጻቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ከሁሉ አስቀድሞ በአጀንዳዎቻችን ላይ እንተማመን፣ በችግሮቻችን መፍቻ መንገድ ላይ እንግባባ” አቶ ግዛቸው ሙሉነህ
Next article“የግል ትምህርት ቤቶች ሀገር ወዳድ፣ ሀገር አሻጋሪ ዜጋ ለመፍጠር ሚናቸውን እንዲወጡ እየተሠራ ነው”- የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የግል ትምህርት ቤቶች ማኅበር