በሰሜን ጎንደር ዞን ምዕራብ ጠለምት ወረዳ ለዘንድሮው የችግኝ ተከላ ከ500 ሺህ በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡

75

ደባርቅ: ሰኔ 30/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በወረዳው በ5 የችግኝ ማዘጋጃ ጣቢያዎች ለማዘጋጀት ከታቀደው 538 ሺህ ችግኝ ውስጥ 528 ሺህ የሚኾነው ተዘጋጅቷል።

ከተዘጋጁት ችግኞች 23 ሺህ የሚኾኑት የፍራፍሬ ችግኞች መኾናቸውን የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ስለሽ በርሔ ለአሚኮ ገልጸዋል።

የችግኝ ዝግጅቱ በሕዳር/2015 ዓ.ም የተጀመረ ሲኾን ለ348 ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉንም ኀላፊው አስረድተዋል።

ዘጋቢ፡- ተስፋየ አይጠገብ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአገልግሎት አሰጣጡ ለብልሹ አሠራር እንዲጋለጥ መንስኤ ሆነዋል ያላቸውን ሠራተኞቹን ከሥራ ማገዱን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።
Next articleሂጅራ ባንክ የሀብት መጠኑ 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር መድረሱን ገለጸ።