የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

68

ባሕር ዳር: ሰኔ 28/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ7 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል።

የድጋፍ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ሮላንድ ኮቢያ ተፈራርመዋል።

ኅብረቱ ድጋፉን ያደረገው ኮሚሽኑ እያከናወነ ያለው ሀገራዊ ምክክር በውጤት እንዲጠናቀቅ በማለም ነው።

በስምምነቱ የአውሮፓ ኅብረት አባል አገራት እና የዓለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ሥራና ስልጠና መምሪያ ከ25 ሺ በላይ ለሚኾኑ ወጣቶች የሥራ እድል መፍጠሩን አስታወቀ ።
Next article“የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሀገር አቀፍ ፈተና ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲዎች ሲሄዱ የአካባቢያቸው አምባሳደር መኾን አለባቸው” የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ