በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ የ2015 ሻምፒዮን ኾነ

63

ባሕር ዳር: ሰኔ 25/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ጨዋታ እየቀረው የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መኾኑን አረጋግጧል፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን የ2015 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የኾነው ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 በኾነ ውጤት በማሸነፍ ነው፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስን ከሀድያ ሆሳዕና ያገናኘው የ29ኛ ሳምንት ጨዋታ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን የኾነባቸውን ግቦች ቸርነት ጉግሳ እና እስማኤል ኦሮ አጎሮ አስቆጥረዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየጣና ሞገዶቹ ሀዋሳ ከተማን አሸነፉ።
Next articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አርባምንጭ ከተማ ገቡ።