ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጌዴኦ ዞን ወናጎ ከተማ ገቡ።

168

ባሕር ዳር: ሰኔ 26/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጌዴኦ ዞን ወናጎ ከተማ ገብተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወናጎ ከተማ ሲገቡ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳ፣ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወናጎ ቆይታቸው የሁለተኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አካል የሆነ ችግኝ ተከላ እንደሚያከናውኑ ይጠበቃል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን 5 ሺህ 368 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና እየወሰዱ መኾኑን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አሰታወቀ።
Next articleየአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ባለፉት አምስት ወራት የተሠሩ ሥራዎችን በኮምቦልቻ ከተማ እየገመገመ ነው፡፡