“በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

94

ባሕር ዳር: ሰኔ 25/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ ትናንት የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሁሉም ዜጎችና ተቋማት ተሳትፎ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ “ትምህርት ለትውልድ” ንቅናቄንም አስጀምረዋል።

ያለትምህርት መስፋፋት በመጪው ዓለም ተወዳዳሪ መኾን ስለማንችል ስለትምህርት ዛሬ የሚጠበቅብንን ልንወጣ ይገባልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናን ከሰኔ 26 እስከ 27/2015 ዓ.ም ባሉት ቀናት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራው ተጠናቋል።
Next article“ጤና ሚኒስቴር ባካሄደው የጤና ጣቢያዎች ውድድር የምሥራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ 2ኛ ደረጃን ይዟል፡፡” የምሥራቅ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ኀላፊ መልካሙ ጌትነት