የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ መሪዎች በብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራምና መሠረታዊ እሳቤዎች ላይ እየተወያዩ ነው፡፡

274

ባሕር ዳር፡ ሕዳር 26/2012ዓ.ም (አብመድ) በምሥረታ ሂደት ላይ የሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራምና መሠረታዊ እሳቤ ላይ እየተወያዩ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ሚንስትሮች፣ ሚንስትር ዴኤታዎች እና ሌሎችም ከፍተኛ ባለስልጣናት ናቸው፡፡

በውይይቱ ኢሕአዴግ የነበሩት መልካም ልምዶችና ክፍተቶች እየተነሱ የሚታረሙበት አግባብ ተመላክቷል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ እውነተኛ የፌዴራሊዝም ሥርዓት እውን የሚሆንበት እንደሆነም በውይይቱ ተነስቷል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ በፕሮግራሙ ጠንካራና ቅቡልነት ያለው ዘላቂ መንግሥታዊ መዋቅርና ተቋማት መገንባት፣ የብሔር ማንነትና ሀገራዊ አንድነት ሚዛን የጠበቀ ማድረግ፣ አንድ ጠንካራ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ መፍጠር ዓላማዎቹ እንደሆኑ ተነስቷል፡፡

የውጭ ጉዳይ እና የፖለቲካል ኢኮኖሚ ጉዳዮች በብልጽግና ፓርቲ ዕይታም ውይይት እየተደረገባቸው ነው፡፡

ዘጋቢ፡- ጽዮን አበበ -ከአዲስ አበባ

Previous articleየቤዛዊት ተገጣጣሚ የሕንጻ አካል ማምረቻ በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ መግባቱ ተገለጸ፤ ፋብሪካው በርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተጎብኝቷል፡፡
Next articleየሠላም ጉዳይ በመንግሥት ብቻ የሚረጋገጥ ባላመሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ አሳሰቡ፡፡