የሽጋው ሞጣ ጠቅላላ ሆስፒታል የ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የፅኑ ሕክምና መሣሪያወች ድጋፍ ተደረገለት።

40

ባሕር ዳር: ሰኔ 23/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የሽጋው ሞጣ ጠቅላላ ሆስፒታል ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የሕክምና መሣሪያች ድጋፍ ተደርጎለታል።

የሕክምና መሣሪያዎች ሆስፒታሉ የአዋቂዎች ፅኑ ሕክምና አገልግሎት ክፍልን ለማስጀመር የሚያግዙ ናቸው። ለፅኑ ሕክምና ወደ ሌላ ተቋማት ሪፈር የሚባሉ ሕመምተኞችን በተወሰነ መልኩ ይቀንሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ሆስፒታሉ ከሚያገለግለው የሕዝብ ቁጥር አንፃር አሁን ላይ በድጋፍ መልኩ የተገኘው የአዋቂዎች የፅኑ ሕክምና መሣሪያወች በቂ ባለመሆናቸው እና በፅኑ ከታመሙት ታካሚዎች መካከል ሞት፣ የሕመምን ሪፈርን እና እንግልትን ለመቀነስ ከጤና ቢሮ እና ከኅብረተሰቡ ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ሆስፒታሉ ጠይቋል።

ሞኒተሪንግ ማሽን ፣ መካኒካል ቬንትሌተር፣ ሰክሽን ማሽን

፣ ፖርቴብል አልትራሳውንድ ፣ የታካሚ አልጋዎች እና ዊልቸር የሕክምና መሣሪያዎች ለሆስፒታሉ ድጋፍ መደረጋቸውን ከሆስፒታሉ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበክምር ድንጋይ ከተማ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተመረቁ ነው።
Next articleወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር በመተባበር የ2 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የሚገመት መድኃኒት ለደሴ ከተማ፣ ለደቡብ እና ለሰሜን ወሎ ዞኖች ድጋፍ አደረገ።