“በትምህርት ላይ የምንሠራቸው ሥራዎች ወጣቶቻችን በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ ለመጓዝ የሚያስፈልጋቸውን ዕውቀት እና ክህሎት እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

30

ባሕር ዳር: ሰኔ 22/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ በትምህርት አቅርቦት ውስጥ አካታችነትን ለማጎልበት በምታደርገው ጥረት የሥርዓተ ጾታ ክፍተቱ እንዲዘጋና ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች የሚያስፈልጋቸውን እንዲያገኙ የሚቻለው ሁሉ እየተደረገ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

በተጨማሪም ለአርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች መሠረተ ልማት እና የትምህርት አገልግሎቶችን ማስፋፋት፤ መደበኛ ያልሆነ ትምህርት እና የሥልጠና መርሐ ግብሮችን ለዐዋቂዎች መስጠት እና የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ለአካል ጉዳተኞች ምቹ መሆኑን ማረጋገጥ ከሚሠሩ ዋና ዋና ሥራዎች መኾናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሳታውቀዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዓለም አቀፉ የትምህርት ትብብር ድርጅት የመጀመሪያ ልዩ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው ።
Next article“ኢትዮጵያ አካታች የትምህርት ስርዓትን በመከተል ሁሉም ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሠራች ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ