የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በጅግጅጋ ከተማ እየተከበረ ነው።

98

ባሕር ዳር: ሰኔ 21/2015 ዓ.ም (አሚኮ) 1 ሺህ 444ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሐመድ በተገኙበት በጅግጅጋ ስታዲየም በድምቀት እየተከበረ ነው።

በዓሉ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶች ነው እየተከበረ እንደሚገኝ ኢቢሲ ዘግቧል።

በአከባበር ስነ-ስርዓቱ ሰላት እና ተክቢራን ጨምሮ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶች በመከናወን ላይ ናቸው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article1ሺህ 444ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሐረሪ ክልል በኢማም አህመድ ስታድየም እየተከበረ ነው።
Next articleየዒድ አል ዓድሃ አረፋ በዓል በአፋር እየተከበረ ነው።