የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

87

ባሕር ዳር: ሰኔ 18/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረጉት ጨዋታ በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው የ28ኛ ሳምንት መርሐ ግብር 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫውተዋል፡፡

በተጠባቂው ደርቢ ጨዋታም ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

ለቅዱስ ጊዮርጊስን እስማኤል ኦሮ አጎሮ 66ኛው ደቂቃ ላይ ግቧን ሲያስቆጥር ለኢትዮጵያ ቡና ደግሞ ብሩክ በየነ በ72ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበክረምት በጎ ፈቃድ 108 ሺህ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ ታቅዷል።
Next articleየ2015 ዓመት የአማራ ክልል እግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና በወልድያ ከተማ እየተካሄደ ነው።