አቶ ይርጋ ሲሳይ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መሥተዳድር የሕዝብ ግንኙነትና የአደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ ኾነው ተሾሙ።

221

ባሕር ዳር: ሰኔ 18/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ሹመት ሰጥተዋል። ርአሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መሥተዳድር የሕዝብ ግንኙነትና የአደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ ሹመት የሰጡ ሲሆን አቶ ይርጋ ሲሳይን ከሰኔ 17/2015 ዓ.ም ጀምሮ የዘርፉ ኃላፊ አድርገው ሹመዋል።

ርእሰ መሥተዳድሩ የሕዝብ ግንኙነትና የአደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ አድርገው የሾሟቸው አቶ ይርጋ ሲሳይ በተለያዩ የሕዝብ፣ የመንግሥትና የፓርቲ አደረጃጀቶች የረዥም ጊዜ ልምድ ያላቸው መሆኑ ታውቋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleወልድያ ዩኒቨርሲቲ በጥገኛ ተዋህስያን ምክንያት በእንስሳቶች ላይ በሽታ እንዳይከሰት የቅድመ መከላከል ሕክምና እየሰጠ ነው።
Next articleበሕገወጥ የወርቅ ምርት፣ ግብይትና ዝውውር ተሳትፎ የነበራቸው የመንግሥት ሐላፊዎችና የጸጥታ መዋቅር አመራሮች በቁጥጥር ሥር ዋሉ