ደብረ ብርሃን የሚገኘው የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከ250 በላይ ለሚደርሱ ወገኖች የሥራ እድል መፍጠሩን ገለጸ።

234

ባሕር ዳር: ሰኔ 15/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባው የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ሚኒ ባስ መኪኖችን መገጣጠም መጀመሩን አስታውቋል።

ፋብሪካው በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሚኒባስ፣ መለስተኛ አውቶቡስ እና የከተማ አውቶቡስ ተሽከርካሪዎችን የማምረት አቅም አለው።

ፋብሪካው በመጀመሪያ ዙር 216 በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ሚኒ ባስ መኪኖችን ከደብረ ብርሃን በተጨማሪ ገላን በሚገኘው መገጣጠሚያው መገጣጠም መጀመሩን ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። በደብረ ብርሃን ከተማ በተገነባው ፋብሪካ በአሁኑ ሠዓት ከ250 በላይ ለሚደርሱ ወገኖች የሥራ እድል መፍጠር ተችሏል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በፓሪስ በአዲስ የዓለም አቀፍ ፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ነው
Next articleአሳሳቢው የትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ ጉዳይ!