ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በፓሪስ በአዲስ የዓለም አቀፍ ፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ነው

94

ባሕር ዳር: ሰኔ 15/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ከልዑክ ቡድናቸው ጋር በፈረንሳይ ፓሪስ በአዲስ የዓለም አቀፍ ፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ባወጣው መረጃ “ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ከልዑክ ቡድናቸው ጋር ፈረንሳይ ፓሪስ በአዲስ የዓለም አቀፍ ፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ነው” ብሏል።

በጉባዔው ላይ የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ የሳዑዲ ዓረቢያ ልዑል አልጋወራሽ ሙሐመድ ቢን ሰልማንን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአፍሪካ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን በፍትሐዊነት መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት እየተካሄደ ነው።
Next articleደብረ ብርሃን የሚገኘው የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከ250 በላይ ለሚደርሱ ወገኖች የሥራ እድል መፍጠሩን ገለጸ።