በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን የምዕራብ ጠለምት ወረዳና የማይጠብሪ ከተማ ነዋሪዎች የማንነት ጥያቄያቸው ሕጋዊ እንዲሆን በሰላማዊ ሰልፍ ጠየቁ።

419

ደባርቅ: ሰኔ 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን የምዕራብ ጠለምት ወረዳና የማይጠብሪ ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ “የጠለምት አማራ ማንነት ጥያቄ የፍትሕ ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጥያቄ ነው” ብለዋል።

ነዋሪዎቹ ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ የተለያዩ መፈክሮችንም አሰምተዋል።

ሕወሓት ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ በኀይል አካባቢውን ወደ ትግራይ አካሎት የቆየ መኾኑን ያነሱት ነዋሪዎቹ በአሁኑ ጊዜ አካባቢው ግፍ ሲፈጽምበት ከነበረው አገዛዝ ላለፉት ሰላሳ ዓመታት በዱር በገደሉ በመታገል ነጻ መውጣቱን አስገንዝበዋል።

የማንነት ጥያቄያቸው ሕጋዊ ኾኖ የአካባቢያቸውን ሰላምና ልማት እንዲያስቀጥሉም መንግሥት ምላሽ እንዲሠጣቸው ጠይቀዋል።

ዘጋቢ፦ ተስፋዬ አይጠገብ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የሚገጥሙንን ሀገራዊና ክልልላዊ ፈተናዎች ለመሻገር ህብረ ብሔራዊ ፌዴራሊዝምን በተገቢው መንገድ መተግበር ይገባል” ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ
Next articleአማራ ባንክ አንድ ዓመት ሞላው! በዚህ አንደኛ ዓመት በዓላችን በውስጥ አቅም የበለጸገውን የሞባይል ባንክ መተግበሪያ ወደ እናንተ ስናቀርብ በደስታ ነው፥ ABa Mobile Banking ከፕሌይ ስቶር በማውረድ የባንካችንን ዲጂታል ዓለም ይቀላቀሉ።