ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ለሩሲያ መንግሥት ልዩ እውቅና ሰጠ።

395
Made with LogoLicious Add Your Logo App

ባሕር ዳር: ሰኔ 04/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የቀድሞው የሶቬት ኅብረት የአሁኗ ሩሲያ ለባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ መመሥረትና ዘመናዊ ትምህርት በኢትዮጵያ እንዲስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጋለች።

በዘመነ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የቀድሞዋ ሶቬት ኅብረት የአሁኗ ሩሲያ በሀገሪቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም እንዲገነባ ከፍተኛ ድጋፍ አድርጋለች።

ዩኒቨርሲቲው ለሩሲያ የሰጠውን እውቅና በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ትርኪሂን ተቀብለዋል።

ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ44 ሀገራት ኤምባሲዎች፣ ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽንና ለሌሎች የሚዲያ ተቋማት፣ ለተለያዩ ተቋማት፤ ለቀድሞ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ሰጥቷል።

ዘጋቢ:- ታርቆ ክንዴ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ከሠላም የተሻለ አማራጭ የለንም” የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ
Next articleባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ እና የሩሲያ ኢምባሲ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ።