አትሌት ለሜቻ ግርማ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረ።

143

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) አትሌት ለሜቻ ግርማ ትላንት ምሽት በፓሪስ በተካሄደዉ ዳይመንድ ሊግ ውድድር የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ሩጫ ውድድር የዓለም ክብረወሰን በመስበር አሸንፏል።

7:52.11 በሆነ ደቂቃ የገባው ለሜቻ ግርማ በሳይፍ ሳኢድ ተይዞ የነበረውን ሪከርድ ከአስራ ስምንት ዓመታት በኋላ የግሉ ማድረጉን ከዓለም አትሌቲክስ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ሌላኛው በርቀቱ የተካፈለው ኢትዮጵያዊው አትሌት አብርሀም ስሜ 8:10.73 በሆነ ደቂቃ አራተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የዘገየ ፍትሕ እንደተነፈገ ይቆጠራል”
Next article“ለከተማችሁ ሕዝብ ክብርና ለማለያ ፍቅር ብላችሁ የገጠማችሁን ፈተና ሁሉ እየተጋፈጣችሁ አሁን ከደረሳችሁበት ወሳኝ ምዕራፍ ደርሳችኋል።” ድረስ ሳኅሉ (ዶ.ር)