“በቀጣይ 20 ቀናት ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ ይደርሳል” ግብርና ሚኒስቴር

101

ባሕር ዳር: ሰኔ 02/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ግብርና ሚኒስቴር አሁናዊ ሀገራዊ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭትን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫውም በቀጣይ 20 ቀናት ወይንም እስከ ሰኔ 21/2015 ዓ.ም ተጠናቆ ጅቡቲ ወደብ ይገባል ብሏል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ.ር) በሰጡት መግለጫ እ.አ.አ ሰኔ 11፣ 18፣ 25 እና 28/2023 አራት መርከቦች ማዳበሪያውን ያጓጉዛሉ ብለዋል።

ግዢ ከተፈጸመበት 12 ነጥብ 87 ሚሊዮን ኩንታል ውስጥ 6 ነጥብ 25 ሚሊዮን ያህሉ ወደ ሀገር ውስጥ ግብቷል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ 5 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ወደ አርሶ አደሩ ተሰራጭቷል ነው ያሉት፡፡ 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ደግሞ በተለያዩ የኅብረት ሥራ ማኅበራት መካዝኖች ስለመኖሩም አንስተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ የአቅርቦት ክፍተቶች ቢስተዋሉም ቀድመው ለሚዘሩ ሰብሎች ቅድሚያ ሰጥቶ የማሰራጨትና በፍጥነት ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ችግር እንዳለም አንስተዋል።

ዘጋቢ፡- እንዳልካቸው አባቡ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል ዓሣ ሃብት ልማት ጽሕፈት ቤት በዘርፉ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳሰበ።
Next articleእየተበራከተ ያለውን በጎዳና ላይ የሚኖሩ ልጆችን ቁጥር በመደጋገፍ መቀነስ ያስፈልጋል ተባለ።