አሜሪካ ለኢትዮጵያ የ112 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አደረገች።

212

ባሕር ዳር : ሰኔ 1/2015 ዓ.ም (አሚኮ) አሜሪካ በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ስርጭትን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የሚውል ተጨማሪ የ112 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አድርጋለች፡፡

ድጋፉ በአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች የአስቸኳይ ጊዜ የኤች አይ ቪ ኤድስ ማገገሚያ ዕቅድ ፕሮግራም (ፔፕፋር) በኩል የሚተገበር ሲሆን ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2030 ኤች አይ ቪን ለማጥፋት የምታደርገውን ጥረት ለማገዝ የሚውል መሆኑ ታውቋል።

የተደረገው ድጋፍ በኢትዮጵያ በደማቸው ውስጥ ኤች አይ ቪ ለሚገኝ ዜጎች የሚደረገውን እንክብካቤ ለማጠናከር እና በ2030 ኤች. አይ .ቪ ኤድስን ከኅብረተሰብ ጤና ስጋትነት እንዲወጣ ለማድረግ ያግዛል ተብሏል፡፡

አሜሪካ በዚህ ፕሮግራም በኩል ባለፉት 20 ዓመታት በኢትዮጵያ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል የሚውል 3 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጓን የአሜሪካን ኤምባሲ ጠቅሶ ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 3ኛና 4ኛ ዙር የተረክ በጉርሻ ባለዕድሎችን ሸለመ።
Next articleየፍሪላንሰር ቅጥር ማስታወቂያ