“አዲስ አበባ የኪነ ጥበብ አቅሟን ማሳደግና ለጎብኝዎች መዳረሻነት መብቃት እንድትችል መሥራት ይገባል” አቶ ሰርጸ ፍሬ ስብሃት

64

ባሕር ዳር: ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (አሚኮ) 14ኛው ከተማ አቀፍ የኪነጥበብ ሳምንት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ግዮን ሆቴል ተከፍቷል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ባሕል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የኪነጥበብ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኀላፊ ሰርፀ ፍሬ ስብሀት አዲስ አበባ ላይ በኪነጥበብ ዘርፉ በስፋት መሥራት ይገባል ብለዋል።

በርካታ የኪነጥበብ ሙያተኞችን ያፈራችው እና የዲፕሎማት ከተማዋ አዲስ አበባ በኪነ ጥበብ ዘርፉም የጎብኝዎች መዳረሻ እንድትኾን መሠራት አለበት ተብሏል።

ምክትል ቢሮ ኀላፊው አዲስ አበባ ከዓለም አቀፍ መድረኮችና ከታላላቅ ፌስቲቫሎች ልምዶችን መቅሰም እንዳለባት አንስተዋል። የኪነ ጥበብ ዘርፉም ልዩ ኢንቨስትመንት ይጠይቃል ነው ያሉት። በዚህ ፌስቲቫልም በርካታ የኪነጥበብ ሥራዎች ይተዋወቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዘጋቢ፡- እንዳልካቸዉ አባቡ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የዲጂታል ነዳጅ ግብይቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገባው ነዳጅ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ያስቻለ ኾኗል” የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
Next articleበአማራ ክልል ወረዳዎች መጋዝን ውስጥ የተቀመጠ የአፈር ማዳበሪያ በፍጥነት ለአርሶ አደሩ በፍትሀዊነት እንዲሠራጭ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።