ወጣቱም በስሜትና አሉባልታ እየተነዳ ጥፋት ከመሥራት መቆጠብ እንዳለበት የአማራ እና ኦሮሚያ የሀገር ሽማግሌዎችና ምሁራን ተናገሩ፡፡

140

ባሕር ዳር፡ ሕዳር 13/2012 ዓ.ም (አብመድ) ወጣቶች የጥፋት ኃይሎች አጀንዳ ማስፈጸሚያ እንዳይሆኑ ወላጆች መምከር እንደሚገባቸውም አሳስበዋል፡፡

ኢትዮጵያ የምትታወቀው በኅብረ ብሔራዊነት እና አንድነት ዜጎች ተከባብረዉ የሚኖርባት ሀገር በመሆን እንደሆነ ነው ምሁራኑና የሀገር ሽማግሌዎቹ የገለጹት፡፡ ‹‹በዚህ ወቅት ያጋጠማት ፈተና ግን ከኢትዮጵያውያን እሴት ያፈነገጠ ነው›› ብለዋል የሁለቱ ክልሎች የሀገር ሽማግሌዎች እና ምሁራን፡፡

ሠላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን በማመላትም ሁሉም ስለሠላም ሊዘምርና ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ‹‹አንዱ ለሌላው ሰው በመሆኑ ብቻ ሊያስብለትና ሊቆረቆርለት ግድ ይለዋል፤ ወጣቱ በስሜትና አሉባልታ እየተነዳ ጥፋት ከመሥራት ሊቆጠብ ይገባል›› ሲሉም መክረዋል፡፡

ዘጋቢ፡- በለጠ ታረቀኝ -ከአዲስ አበባ

Previous articleየንጉሥ ተክለሃይማኖት ቤተ መንግሥትና በውስጡ ያሉ ቅርሶች ታሪክ መስካሪ መሆናቸው ቀርቶ ታሪክ እንዲሆኑ ስለምን ተፈረደባቸው?
Next articleበአጣየ ከተማ የእርቀ ሠላም ሥነ ስርዓት እየተካሄደ ነው፡፡