“የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ይሰጣል” ትምህርት ሚኒስቴር

525

ባሕር ዳር: ግንቦት 10/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ግንቦት 10/2015 ዓም. (የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን አሳውቋል።

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል ነው ያለው ሚኒስቴሩ።

ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል አምራች እና ሸማች የሚገናኙበት 34 የገበያ ማዕከላት ለይተናል” የአማራ ክልል ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ
Next article“የአማራ ሕዝብ ጥያቄዎች የሚፈቱት በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር በመኾኑ ወጥ አቋም ይዞ መታገል ይገባል” ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር)