“ለመኸር ምርት ከ8 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሜትር ኩዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቷል” የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ

52

ደብረ ብርሃን:ግንቦት 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ላለፋት ተከታታይ ዓመታት ካጋጠሙ የሰው ሠራሽ ማዳበሪያዎች እጥረት ትምህርቶችን በመውሰድ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን መምሪያው አስታውቋል::

የመምሪያው የሰብል ልማት ባለሙያ ተውልኝ ሽባባው እንደአለፉት ዓመታት ሁሉ ለመጭው የመኸር ወቅትም ዞኑ ሊያዘጋጀው ከሚጠበቀው የሰው ሠራሽ ማዳበሪያ ውስጥ ዘገባው እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ 50 ነጥብ 2 በመቶ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡

ባለሙያው እንደሚሉት ካለፉት ዓመታት ትምህርት በመውሰድ ለ2015/16 የመኸር ምርት 8 ሚሊዮን 186 ሺህ 652 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት በመቻሉ እጥረቱን ማቃለል ተችሏል፡፡

ከተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ውስጥም 1 ሚሊዮን 956 ሺህ 207 ሜትር ኩዩቢ ጥቅም ላይ መዋሉን ነው ያስረዱት፡፡

በዞኑ በመጭው የመኸር ዘመን 498 ሺህ 758 ሄክታር መሬትን በሰብል ለመሸፈንና ከዚህም 17 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ባለሙያው ተናግረዋል፡፡

የምርት ዘመኑን በታቀደው  መሠረት ለመፈጸም የምርጥ ዘር ዝግጅት፣ የተባይና መጤ አረሞች ቅድመ መከላከል ሥራዎች ከወዲሁ በቅንጅት እየተሠሩ ስለመሆኑም ባለሙያው ገልጸዋል።

ዘጋቢ፡- ሥነ-ጊዮርጊስ ከበደ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሚሊዮኖች ጎብኝተውታል፣ ቢሊዮን ብሮች ተገኝቶበታል”
Next article“በማሣው ላይ የተሠራውን እርከን በፍሬ የሞላው ጀግና አራሽ”