ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የግብርና እና ሳይንስ አውደ ርዕይን መርቀው ከፈቱ።

102

ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 29/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በግብርና ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የግብርና እና ሳይንስ አውደ ርዕይን በሳይንስ ሙዚየም መርቀው ከፍተዋል።

አውደ ርዕዩ የምርታማነት ቴክኖሎጂ ፣ የምርምርና ፈጠራ ስራዎች ፣ ዲጂታላይዜሽን ግብርና እና የግብርና ፋይናንስ ላይ ያተኮረ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ የሚቀርብበት ነው።

በግብርና ሚኒስቴር ፣ በኢትዮ ቴሌኮም እና በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ”ከቤተ ሙከራ ወደ አዝመራ ” በሚል መሪ ሀሳብ መካሄድ የጀመረው አውደ ርዕዩ 70 የውጭና የሀገር ውስጥ በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ምርቶቻቸውን እና የግብርና ቴክኖሎጂዎቻቸውን ለዕይታ አቅርበዋል።

ከዚህ በተጨማሪም፣ አውደ ርዕዩ በፓናል ውይይት እና በተለያዩ ዝግጅቶች የግብርና ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም ሌሎች የግብርና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይካሄዳል።

ኢቢሲ እንደዘገበው፤ በአውደ ርዕዩ ላይ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህን ጨምሮ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች ተገኝተዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየክልሉን ሕዝብ ሰላም ለማፅናት እና አንድነቱን ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ስምምነት ላይ መድረሱን በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።
Next article“የኢኮኖሚያችንን ምንጭ ዘግተን፤ የድህነትን በር በመክፈት የምናሸንፈው ጠላት አይኖርም!” የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ጽሕፈት ቤት