የኢንፎርሜሽን መረብ ደኀንነት አሥተዳደር ባለፉት 9 ወራት የሳይበር ጥቃት ሙከራን የመመከት አቅሙ 94 ነጥብ 8 ከመቶ መድረሱን አስታወቀ፡፡

45

አዲስ አበባ: ሚያዝያ 26/2015 ዓ.ም (አሚኮ)የአሥተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ሶካ የሳይበር ጥቃት ኢላማ ከተደረጉ ተቋማት መካከል ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት፣ የጸጥታና ደኀንነት ፣ የሚዲያና ሌሎች የመንግሥት ቁልፍ ተቋማት ይገኙበታል ብለዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደኀንነት አሥተዳደር የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኀንነት አሥተዳደር ባለፉት 9 ወራት የሳይበር ጥቃቶችን በመከላከል 19 ቢሊዮን ብር ማዳን መቻሉ ተገልጿል። በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሀገራችን 4 ሺህ 422 የሳይበር ጥቃቶችን እና የጥቃት ሙከራዎች የተፈጸሙ መኾኑን ገልጿል። ከእነዚህ መካከል 4 ሺህ 272 ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሂደት ላይ መኾናቸውን ነው ዋና ዳይሬክተሩ ሰለሞን የተናገሩት። ጥቃቶቹ ቢደርሱ ኖሮ የመሠረተ ልማቶች መቋረጥ፣ ተቋማት የሚሰጧቸው አገልግሎቶች መስተጓጎልና የገቢ መስተጓጎል ይደርስ ነበር ተብሏል።

ዘጋቢ፡- ድልነሳ መንግሥቴ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየጀርመን መራሔ መንግሥት ኦላፍ ሾልዝ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ።
Next articleየኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር ከሱዳን ተፈናቅለው በመተማ ዮሐንስ ከተማ ተጠልለው ለሚገኙ ወገኖች ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ።