የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ሠላማዊ መማር ማስተማር ለመፍጠር እየመከሩ ነው፡፡

373

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሠላማዊ የመማር ማስተማር እና መልካም አስተዳድርን ለማስፈን እየተሠሩ ባሉ ሥራዎች ዙሪያ ነው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሪዎች እየተወያዩ ነው፡፡

ሁሉንም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ነባራዊ ሁኔታ ማዕከል ባደረገ መልኩ የለውጥ ሥራ አመራር፣ የመልካም አስተዳደር የአሠራር እና የአደረጃጀት መመሪያ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ማዘጋጀቱን ነው በጉባኤው የገለፁት።

መመሪያው በመንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠላማዊ የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማኅበርሰብ አገልግሎት ተልዕኮዎችን በላቀ ሁኔታ መፈፀም የሚያስችል መሆኑም ተመላክቷል።

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለከፍተኛ የትህምርት ተቋማት ሠላማዊ የመማር መስተማር እና የመልካም አስተዳድር ሥራዎች ስኬታማነት ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግም ተገልጿል፡፡

በውይይቱ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና ከ45 በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ነው።

Previous articleበህዳሴ ግድብ ዙሪያ የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ የውኃ ሚኒስትሮች እየተወያዩ ነው።
Next articleአንድ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲው ዓለም ሲቀላቀል ትልቅ ጉዳይ በመያዝ ነው፤ እሱም ለወደፊት የሚኖረው ተስፋ እና የዕድገት ራዕይ ነው፡፡