“ሞት በእውነተኛ ሰዎች ላይ እንጅ በእውነት ላይ ስልጣን የለውም” አቶ ግርማ የሽጥላ

218

የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ የነበሩት የአቶ ግርማ የሺጥላ የህይዎት ታሪክ።

➨ግርማ የሺጥላ ከአባታቸው ከአቶ ሺጥላ ወልደጻድቅ ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘውዴ ስመኝ በቀድሞ ሸዋ ክፍለሀገር በመንዝ ግሽ አውራጃ በጌራ ምድር ወረዳ ማሀል ሜዳ ከተማ ሕዳር 17/1967 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
➨የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በማሀል ሜዳ አጠናቀዋል፡፡
➨በዲፕሎማ በማኜጅመንት ተመርቀዋል፡፡

➨የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ አግኝተዋል፡፡ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በኮተቤ ሜትሮ ፖሊታንት ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ ተመርቀዋል፡፡
➨ሰኔ 1986 በአማራ ክልል ሰሜን ሽዋ ዞን በአንጾኪያ ወረዳ የተፈጥሮ ሀብት ጽሕፈት ቤት ባለሙያ ኾነው ሠርተዋል፡፡
➨1989 ጀምሮ እስከ 1990 ዓ.ም ድረስ በአማራ ክልል ሰሜን ሽዋ ዞን በአንጾኪያ ወረዳ የኢኮኖሚ ዘርፍ ሥራ አሥፈጻሚ በመኾን አገልግለዋል፡፡
➨1990 ዓ.ም እስከ መስከረም 1995 ዓ.ም የአንጾኪያ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ በመኾን አገልግለዋል፡፡

➨1995 ዓ.ም የሰሜን ሽዋ ዞን ብአዴን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ኾነውም አገልግለዋል፡፡
➨ከመስከረም 1997 ዓም እስከ ሕዳር 30/1998 ዓ.ም የደብረብርሃን ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የማስታወቂያ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ በመኾን ሠርተዋል፡፡
➨ታኅሣሥ 1/1998 ዓ.ም ጀምሮ በሰሜን ሽዋ ዞን የባሶና ወረና የማስታወቂያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመኾን ሠርተዋል

➨ሚያዚያ 1/1999 እስከ መስከረም 2000 ዓ.ም ድረስ የሰሜን ሽዋ ዞን የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ ኾነው ሰርተዋል፡፡
➨የሰሜን ሽዋ ዞን የብአዴን ጽሕፈት ቤት የሕዝብ አደረጃጀት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኾነውም ሠርተዋል፡
➨እስከ መስከረም 2008 ዓ.ም ደግሞ የሰሜን ሽዋ ዞን ምክትል አሥተዳዳደሪ በመኾንም ሠርተዋል፡፡

➨ከጥቅምት 1/2008 ዓ.ም ጀምሮ የሰሜን ሽዋ ዞን አሥተዳዳደሪ በመኾንም ሠርተዋል፡፡
➨በ2013 ዓ.ም የአማራ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ኀላፊ ኾነው አገልግለዋል፡፡
➨ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ ሕይወታቸው አስካለፈበት ቀን ሚያዝያ 19/2015 ዓ.ም ጀምሮ የብልጽግና ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ብልጽግና ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ በመኾን አገልግለዋል፡፡

➨በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በባሶና ወረና ወረዳ የቀይት ምርጫ ጣቢያ በመወዳደር ሕዝባቸውን ወክለው ሲሠሩም ቆይተዋል፡፡
➨የአማራ ክልልን በመወከልም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል ኾነው ሠርተዋል፡፡

➨ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ፣የደብረ ብርሃን ሪፈራል ሆስፒታል እና የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽኝ ሥራ አመራር ቦርድ ኀላፊ ኾነውም ሠርተዋል፡፡
➨አቶ ግርማ የሽጥላ በ48 ዓመታቸው በተፈጸመባቸው ግድያ ህይዎታቸው አልፏል፡፡

➨አቶ ግርማ የሺጥላ የ3 ሴቶች እና የ4 ወንድ ልጆች አባትም ነበሩ፡፡

በምሥጋናው ብርሃኔ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“መላው ሕዝባችን እንዲያውቀው የምንፈልገው ጽንፈኝነት ራሱን በልቶ የሚጨርስ መኾኑን ከሰኔ 15 እና ከሚያዚያ 19 መማር እንደሚቻል ነው” ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር)
Next article“የወንድማችን ገዳዮች መንግሥትና ሕዝብ በመረባረብ ለፍርድ እንዲያቀርቡልን እንጠይቃለን” አቶ ኃይሌ የሽጥላ የአቶ ግርማ የሽጥላ ወንድም