የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል ተመስገን ጥሩነህ የሀዘን መግለጫ

330

በወንድማችን በግርማ የሺጥላ ላይ በተፈጸመው ኢሰብአዊ ድርጊት በእጅጉ አዝኛለሁ። የዚህ አሰቃቂ ድርጊት ዓላማ ለሀገር የሚሠሩትን ማሸማቀቅ ነው። ግን አይሳካም። ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን የኢትዮጵያ ጉዞ አይገታም።

ይሄንን ኢሰብአዊ ድርጊት የፈጸሙትን አካላት ለፍርድ ለማቅረብ እየሰራን ነው። ኢትዮጵያ የጽንፈኞች ሀገር እንዳትሆንም ሕግ ማስከበራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
ለጓዶቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ፣ ቤተሰቦቹ እና ለመላው ሕዝብ መጽናናትን እመኛለሁ።

Previous articleየአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ መሬት ቢሮ እና የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በአቶ ግርማ የሺጥላ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ።
Next article“በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ የፅንፈኛ ኃይሎቹን ትክክለኛ መልክና ገፅታ ለሕዝቡ በይፋ ያጋለጠ ነው” የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል