የኢትዮ ቴሌኮም ማዕከላዊ ሰሜን ሪጅን ሠራተኞችና አጋር ድርጅቶች ለተፈናቃዮች ድጋፍ አደረጉ::

76

ደብረ ብርሃን: ሚያዝያ 19/2015 ዓ.ም (አሚኮ)የኢትዮ ቴሌኮም ማዕከላዊ ሰሜን ሪጅን ሠራተኞችና አጋር ድርጅቶች ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን የተፈናቃዮች ጣቢያ ለሚገኙ ዜጎች ድጋፍ አድርገዋል::
የማዕከላዊ ሰሜን ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ከተማ ዳዲ ከሪጅኑ ቋሚና ኮንትራት ሠራተኞች እና ከሪጅኑ አጋር ድርጅቶች በተሰበሰበ 406 ሺህ ዘጠኝ መቶ ብር የጤፍ ዱቄት ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል::

ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን ቻይና ካምፕ ተብሎ በሚጠራው የተፈናቃዮች ጣቢያ ለሚገኙ 240 አቅመ ደካሞች ድጋፉ ተሰጥቷል::
ዳይሬክተሩ የተፈናቃዮቹ ቁጥር ከፍተኛ ከመኾኑ አኳያ ድጋፋችን ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ እኛም አጋሮቻችንም ተረድተናል ብለዋል፡፡ ሌሎች መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማትና ግብረ ሰናይ ድርጅቶችም ለተፈናቃዮቹ ትኩረት እንዲሰጡም አሳስበዋል::

ድጋፍ የተደረገላቸው ተፈናቃዮችም ኢትዮ ቴሌኮም እና አጋሮቻቸው ስላደረጉላቸው ድጋፍ አመስግነዋል።

ዘጋቢ፦ ሥነ ጊዮርጊስ ከበደ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከትግራይ ክልል ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ትግራይ ክልል የሚደረገው የየብስ ትራንስፖርት ዛሬ ተጀመረ፡፡
Next article“ትስስርና መስተጋብር በኢትዮጵያ ታሪክ” በሚል ርዕስ የታተመ መጽሐፍ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ተበረከተ።