የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የጉምሩክ ቀረጥና ታክስን በቴሌ ብር መክፈል የሚያስችል የአጋርነት ስምምነት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ተፈራረመ፡፡

156
ባሕር ዳር: ሚያዝያ 12/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በስምምነቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ እንዳሉት የአጋርነት ስምምነቱ ወረቀት አልባ የጉምሩክ አገልግሎቱን ለማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ የአሠራር ዘዴዎችን ለመቀየር እና በዘመናዊ አከፋፈል የከፋይ ጊዜን እንዲሁም ድካምን ለመቆጠብ ያግዛል።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የአጋርነት ስምምነቱ በዋነኛነት የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በዲጅታል የታገዘ የአገልግሎት ሥርዓት በመዘርጋት የታክስና ቀረጥ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመሰብሰብ እንደሚያግዘው ተናግረዋል፡፡ ስምምነቱ የኮሚሽኑ ደንበኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ ትልቅ ሚና እንዳለው ሥራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል፡፡
የጉምሩክ ታክስ እና ቀረጥ ክፋያዎች በቴሌ ብር መደረጉ ለሀገር ከሚሰጠው ጠቀሜታ ባሻገር የሎጂስቲክ አፈጻጸም ጠቋሚ እንዲሻሻልና ለመጋዘን የወደብ ኪራይ የሚከፍሉ ወጭዎችን ለመቀነስ አስተዋፅኦው የጎላ ነው ተብሏል፡፡
ዘጋቢ፡- ራሄል ደምሰው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየአማራ ክልል ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡
Next article“ቢላል የእስልምና ሃይማኖት እንቁ ፣የኢትዮጵያም ኩራት ነው” ሼህ ሙሐመድ አንዋር ጁኔድ